About admin

ኢናብ ቴክ ክፍል 44 – በአውዳሲቲ የማጀቢያ ሙዚቃን ማስተካከል

Play
download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ቲክቶክ የአሜሪካዋን ሞንታና ግዛት ስለመክሰሱ፣ ኒቫ የተባለው የኢንተርኔት መፈለጊያ አገልግሎቱን ማቋረጡን ስለማስታወቁ እና ሞዚላ ፋየርፎክስ ዊንዶውስ 7 እና 8ን እስከወዲያኛው ስለመሰናበቱ የሚሉትን መረጃዎች እንመለከታለን።
በኮምፒውተር ቲፕስ ኤንድ ትሪክስ፣ በአውዳሲቲ ማሳያ የመጨረሻው ክፍል ከስር የሚሰማ ሙዚቃን በአውዳሲቲ ከፍ እና ዝቅ እንዲልልን እንዴት እንደምናደርግ በተግባር እንሞክራለን።
በመሰረታዊ ክፍል፣ የጃውስ ልዩ ልዩ ከርሰሮችን እንዴት እንደምናበራ የምንዳስስ ይሆናል።
በአድማጮች አስተያየትም በማይክሮሶፍት ወርድ ጽሁፍ ከጻፍኩ በኋላ ፎንቱ ልክ አይደለም እየተባልኩ ነው፣ ቶክባክ እንደጂሺዎ አልፈጥን አለኝ፣ ኤንቪዲኤ አኖውን፣ አኖውን እያለ ምንም አያነብልኝም፣ ለሚሉ እና ሌሎች ጥያቄዎች ምላሽ አካትቻለሁ።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሱትን አውዳሲቲን ከዚህአውዳሲቲ ኤንቪዲኤ አድኦንን ከዚህ ያውርዱ።

Monday June 5th, 2023 Podcasts

The 16th Board of the Association handing over power to the 17th board.

The 16th round board of the Association handing over power to the 17th board commenced today June 4th, 2023.

Enab’s pre-election, election and post-election movement, which has been in place over the past six months, was wrapped up in today’s sworn in with the 16th round board of the Association handing over power to the 17th round board.

Today, With the presence of invited guests who have served the association in various positions of employment and leadership positions over the years, and Mr. Wesen, who was the board members of the 16th Addis Ababa Polling Station and the Board of Directors at the 16th Addis Ababa Polling Station, after sharing their experience with the new board members, the new board members have sworn allegiance to serve the Association faithfully and sincerely, signing a power-sharing document from Mr. Ayele Bogale, the association’s current vice president, to the new board.

Left to right, Ato Ayele, Ato Ghebrie, Ato Abera, and Ato Sebeibie
The swearing in ceremony of the 17th round Members of the exceutive board
New elected board members with former members
Monday June 5th, 2023 Uncategorized

ኢናብ ቴክ ክፍል 43 – በአውዳሲቲ ድምጽን ማስተካከል እና ማሳመሪያዎችን መጨመር

Play

download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ሜታ የተባለው የፌስቡክ ባለቤት የሆነው ኩባንያ ትልቅ የተባለውን የ1.5 ቢሊየን ዶላር ቅጣት የተወሰነበት ስለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ሶስተኛውን የቴሌኮም ኩባንያ ወደገበያ ሊያስገባ መሆኑን ስለማስታወቁ፣ ኢንቴል 32 ቢት ፕሮሰሰሮችን ሊያስቀር ማሰቡን እና የታላላቅ ኮምፒውተሮች ዝርዝር ስለመውጣቱ የሚሉትን መረጃዎች እንመለከታለን።
በኮምፒውተር ቲፕስ ኤንድ ትሪክስ፣ ስንቀርጸው ድምጹ ያነሰብንን ክፍል እንዴት ለብቻው ድምጽ መጨመር እንደምንችል እና የገደል ማሚቶ ማሳመሪያን ወደቀረጽነው ድምጽ አጨማመር በአውዳሲቲ በተግባር እናያለን።
በመሰረታዊ ክፍል፣ መሰረታዊ መረጃዎችን እንደሰአት፣ እንደቀን፣ እንደርእስ የመሳሰሉትን ከኮምፒውተራችን እንዴት ጃውስ ተጠቅመን እንደምንጠይቅ በተግባር እየሞከርኩ አሰማችኋለሁ።
በአድማጮች አስተያየትም ስለዶትወከር ለተነሳ ጥያቄ ምላሽ እና የአውዳሲቲ ኤንቪዲኤ አድኦን ዳውንሎድ እምቢ ላላችሁ በአድማጮች አስተያየት በተላከልኝ ግብረመልስ ማስተካከያ አድርጌበታለሁ።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሱትን አውዳሲቲን ከዚህአውዳሲቲ ኤንቪዲኤ አድኦንን ከዚህ ጂሺዎ ትልቁን ከዚህ ያውርዱ።

Wednesday May 31st, 2023 Podcasts

Ethiopian National Association of the Blind (ENAB) has conducted a workshop on the Marrakesh treaty with relevant stakeholders in Addis Ababa City.

Ethiopian National Association of the Blind (ENAB) has conducted a workshop on the Marrakesh treaty with relevant stakeholders in Addis Ababa City.

Ethiopian National Association of the Blind (ENAB) has conducted a workshop on the Marrakesh treaty with relevant stakeholders in Addis Ababa City. Participants from F.D.R.E Ministry of Women and Social Affairs, F.D.R.E Ministry of Innovation of Technology, Ethiopian Intellectual Property Authority, and Ethiopian Writers Association have attended the workshop.

Discussions were made on Information accessibility in the context of United nations Convention on the rights of persons with disabilities (UNCRPD) and the Marrakesh Treaty to Facilitate Access to Published Works for Persons Who Are Blind, Visually Impaired or Otherwise Print Disabled. And way forward was set on the importance of working together in crafting the implementation proclamation (amendment) for the Marrakesh treaty.

Ethiopia have ratified the Convention on the Rights of Persons with Disabilities on July 7, 2010 by ratification Proclamation No. 676/2010, and the and signed the Marrakesh treaty in November 2020. As per Article 9, sub article 4 of the F.D.R.E Constitution “All international agreements ratified by Ethiopia are an integral part of the law of the land.”

Here are major articles from United Nations Convention on the rights of persons with disabilities (UNCRPD) regarding information accessibility.

Article 4.1.g dictated states parties to undertake or promote research and development of, and to promote the availability and use of new technologies, including information and communications technologies, mobility aids, devices and assistive technologies, suitable for persons with disabilities, giving priority to technologies at an affordable cost.

Article 9 dictated States Parties to take appropriate measures to ensure to persons with disabilities access, on an equal basis with others, to the physical environment, to transportation, to information and communications, including information and communications technologies and systems, and to other facilities and services open or provided to the public, both in urban and in rural areas.

Article 21 dictated States Parties shall take all appropriate measures to ensure that persons with disabilities can exercise the right to freedom of expression and opinion, including the freedom to seek, receive and impart information and ideas on an equal basis with others and through all forms of communication of their choice. This includes Providing information intended for the general public to persons with disabilities in accessible formats and technologies appropriate to different kinds of disabilities in a timely manner and without additional cost.

Article 30 Sub article 3 3. Dictates States Parties shall take all appropriate steps, in accordance with international law, to ensure that laws protecting intellectual property rights do not constitute an unreasonable or discriminatory barrier to access by persons with disabilities to cultural materials.

This workshop is conducted as part of the Enabling Capabilities project funded by Danish Association of the Blind.

Sunday May 28th, 2023 News

ኢናብ ቴክ ክፍል 42 – በአውዳሲቲ ኤክስፖርት ማድረግ እና የድምጽ አቀራረጽ

Play

download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ጂሺዎ አዲስ በለቀቀው ቨርዥን ስላሻሻላቸው ነገሮች እንዲሁም ጉግል አካውንታችሁን ለሁለት አመት ካልተጠቀማችሁበት እሰርዘዋለሁ ማለቱን ከነምክንያቱ እነግራችኋለሁ።
በኮምፒውተር ቲፕስ ኤንድ ትሪክስ፣ በአውዳሲቲ አጠቃቀም ያስተካከልነውን ድምጽ እንዴት ኤክስፖርት አድርገን ለራሳችንም ሆነ ለሌላ ሰው እንዲያዳምጠው ማድረግ እንደምንችል እና በኤላላ በኩል ደግሞ ድምጽ እንዴት እንደምንቀርጽ እንመለከታለን።
በመሰረታዊ ክፍል፣ የጃውስን አጠቃቀም በሚያብራራው ዝግጅቴ ጃውስን እንዳይለፈልፍብን እንዴት ዝም እንደምናስብል እና የንባቡን ፍጥነት እንዴት ከፍ እና ዝግ እንደምናደርግ እና ሌሎችንም እንመለከታለን።
በአድማጮች አስተያየትም ስለዶትወከር ፊት እና ኋላችንን እንዴት እንደምናሳውቀው፣ ከመጠን በላይ እንዳይለፈልፍ እንዴት እንደምናደርግ እና ሌሎችንም አካትቼ ቀርቤያለሁ።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሱትን አውዳሲቲን ከዚህአውዳሲቲ ኤንቪዲኤ አድኦንን ከዚህ ጂሺዎ ትንሹን ከዚህ ያውርዱ።

This podcast is powered by Pinecast.

Sunday May 28th, 2023 Podcasts

17th round General Assembly Establishment and 1st round regular meeting of the Ethiopian Association of the Blind held on May 19 & 20, 2013

17th round General Assembly Establishment and 1st round regular meeting of the Ethiopian Association of the Blind held on May 19 & 20, 2013

የስብሰባው አጀንዳ ሆነው ቀርበው የነበሩት፡ 

  1. አጀንዳዎችን አቅርቦ ማጽደቅ
  2. የትግራይ ተወካዮችን ተሳትፎ በተመለከተ ተወያይቶ መወሰን
  3. የጉባኤውን መሪዎች መምረጥ
  4. የማህበሩን ከሐምሌ 1/2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም የ6 ወራት የሽግግር ግዜ ክንውን ሪፖርት መርምሮ መወመሰን
  5. የማህበሩን ከሐምሌ 1/2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም የ6 ወራት የሽግግር ግዜ ሒሳብ መግለጫ እና በውጭ ኦዲተር የተመረመረ የኦዲት ሪፖርት መርምሮ መወሰን
  6. የውስጥ ኦዲተር ስለሚሾምቦት ሁኔታ ተወያይቶ መወሰን
  7. ለህንጻ ግንባታ የሚውል መነሻ ገንዘብ መወሰን
  8. የማህበሩን መተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 17 ትርጉም መስጠት
  9. የማህበሩን መተዳደሪያ ደንብ ስለሚሻሻልበት ሁኔታ ለቦርዱ አቅጣጫ መስጠት
  10. የማህበሩን የቀጣይ 5 ዓመታት መሪ እቅድ ተወያይቶ መወሰን
  11. የማህበሩን የ2023 ዓመታዊ እቅድ እና በጀት መርምሮ ማጽቅ
  12. የአማካሪ ቦርድ መመሪያ መርምሮ መወሰን
  13. የ17ኛ ዙር ስራ አመራር ቦርድ ምርጫ ማከናወን

ናቸው።

አጀንዳ 1. አጀንዳዎችን አቅርቦ ማጽደቅ

ከስራ አመራር ቦርድ 13 አጀንዳዎች ቀርበው ተጨማሪ አስተያየት ካለ ቤቱ ተጠይቆ፡፡

  • የምርጫ አጀንዳ ለምን ተለያይቶ ተቀመጠ?
  • የሪፖርት እና እቅድ የጊዜ ቅደም ተከተላቸው እና የበጀት ዘመኑ አልተዛባም ወይ?
  • አማካሪ ቦርድ ለምን አስፈለገ?
  • የትግራይ ምርጫ በተመለከተ ግልጽ ስላልሆነ ለምን በአጀንዳ ቀረበ?
  • የደንብ ማሻሻል ለምን ለቦርድ ይመራል?
  • የተባባሪ አባላት ቦታ ለክልል ይሰጥ፤
  • ቅርንጫፎች ላይ ከባድ ችግር ስላለ መታየት አለበት፤
  • የቆቦ ምርጫ ጉዳይ ለምን አልተያዘም?
  • አጀንዳ በቅድሚያ በብሬል ለምን አልቀረበልንም?
  • የውስጥ ኦዲተር ሹመት ምን ማለት ነው?

የሚሉ ጥቄዎች እና አስተያየቶች ተነስተው በቦርዱ እና በጽ/ቤቱ ማብራሪያ ከተሰጠ በኋላ በአጀንዳው ላይ በተሰጠው ድምጽ ከስራ አመራር የቀረቡት 13 አጀንዳዎች በሙሉ ድምጽ ጸድቀዋል፡፡

 

አጀንዳ 2. የትግራይ ተወካዮችን ተሳትፎ በተመለከተ ተወያይቶ መወሰን

ከትግራይ ክልል 5 ምርጫ ጣቢያዎች በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ ሊካሄድ ያልቻለ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ አባላቱ ያለተወካይ መቅረት ስለሌለባቸው ቦርዱ የ16ኛው ዙር የትግራይ ተወካዮች በጉባኤው ላይ ለአንድ አመት ከነሙሉ መብታቸው ተገኝተው በአንድ ዓመት ውስጥ ምርጫ እንዲካሄድ፤ አሁን በሚካሄዱት የቦርድና የጉባኤ አመራር ምርጫ ላይ ከትግራይ ከተመረጡና በምርጫ ጣቢያቸው ምርጫ ሲካሄድ ሳይመረጡ ከቀሩ በነሱ ምትክ እንዲሟላ እንዲደረግ ሃሳብና ማብራሪያ ቀርቧል፡፡

ከቤቱ በተሰጠው አስተያየትና ጥያቄ የትግራይ ጉዳይ ደንቡን ተከትሎ መፈጸም ይኖርበታል፤ አንድ ተመራጭ በደንቡ መሰረት የተወሰነ ጊዜ ስላለው ምርጫ መካሄድ ይኖርበታል የሚል አስተያየት ሲሰጥ በሌላ በኩል ለአንድ አመት ብቻ ሳይሆን ለአራቱም አመት እንዲቀጥሉ መደረግ አለበት የሚል አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ቦርዱ ባቀረበው መሰረት ለአንድ አመት ብቻ እንዲራዘም የሚለው የቦርዱ ሃሳብ ላይ የድጋፍ አስተያየት ተሰጥቷል፡፡

በተነሱት ሃሳቦች ላይ በተሰጠው ማብራሪያ ምርጫ ያልተካሄደው በአስገዳጅ ሁኔታ ምክንያት ስለሆነና ይህ ደግሞ በማህበሩ ብቻ ሳይሆን የትግራይ ክልል እራሱ በጊዜያዊ መንግስት የሚመራ ሲሆን፣ ሌሎችም ምርጫ ያልተካሄደባቸው የመንግስት መዋቅሮች ስላሉ ህግ መጣስ አለመሆኑ የተብራራ ሲሆን ለአራት አመት ማስቀጠል ግን የጉባኤው ስልጣን ሳይሆን የመራጩ አባል ስልጣን በመሆኑ እንደማይቻል ተግባብቶ ድምጽ ተሰጥቷል፡፡ በተሰጠውም ድምጽ፡- ከትግራይ ክልል 5 ምርጫ ጣቢያዎች ለ16ኛው ጠቅላላ ጉባኤ አባልነት ተመርጠው ስለነበረ ለአንድ አመት በሙሉ መብታቸው እንዲሳተፉና በአንድ አመት ውስጥ ምርጫ ተካሂዶ የተመረጡት በመደበኛነት እንዲቀጥሉ የሚለው የቦርዱ ሃሳብ ጸድቋል፡፡

አጀንዳ 3.  የጉባኤውን መሪዎች መምረጥ

በመጀመሪያ የአስመራጭ ኮሚቴ ምርጫ ተከናውኗል፡፡ በዚህም መሰረት 5 እጩዎች በፍቃደኝነት ቀርበው በተሰጠው ድምጽ አቶ ለገሰ ሀ/ማርያል 35 አቶ ተስፋው አወቀ 34፤ ወ/ሪት ቃልኪዳን ሽመልስ 32፤ አቶ ጫላ ጉደታ 30፤ አቶ የማነ ዮሃንስ 16፤ ድምጽ አግኝተው ከፍተኛውን ድምጽ ያመጡት አቶ ለገሰ ሃ/ማርያል፣ አቶ ተስፋው አወቀ እና ወ/ሪት ቃልኪዳን ሽመልስ የአስመራጭ ኮሚቴ ሆነው በመካከላቸው ባደረጉት የሃላፊነት ድልድል አቶ ተስፋው አወቀ ሰብሳቢ አቶ ለገሰ ሃ/ማርያም ጸሐፊ ወ/ሪት ቃልኪዳን ሽመልስ አባል ሆነው መድረኩን ተረክበዋል፡፡

በአስመራጭ ኮሚቴው አማካኝነት ለሶስቱ የጉባኤ አመራር አባላት 6 እጩዎች ተጠቁመዋል፡፡ እነሱም አቶ መብራቱ አሰፋ፣ አቶ መሠረት በለጠ፣ አቶ ኤርሚያስ ቃልኣብ፣ ወ/ሪት አበባ ጽጌ፣ አቶ ዮሐንስ ካህሳይ እና አቶ ሀይለልዑል ምስጋናው ተጠቁመዋል፡፡ በተሰጠውም ድምጽ አቶ መብራቱ አሰፋ 36፤ አቶ ሀይለልዑል ምስጋናው 25፤ አቶ መሠረት በለጠ 26፤ አቶ ዮሐንስ ካህሳይ 24፤ ወ/ሪት አበባ ጽጌ 24፤ አቶ ኤርሚያስ ቃልኣብ 14 ድምጽ አግኝተዋል፡፡ በመሆኑም ከፍተኛውን ድምጽ ያገኙት አቶ መብራቱ አሰፋ ፣ አቶ መሠረት በለጠ እና አቶ ሀይለልዑል ምስጋናው የጉባኤው መሪዎች ሆነው ተመርጠዋል፡፡ በመካከላቸው ባደረጉትም የሃላፊነት ድልድል አቶ መብራቱ አሰፋ ሰብሳቢ፣ አቶ መሠረት በለጠ ምክትል ሰብሳቢ፣ አቶ ሀይለልዑል ምስጋናው ጸሐፊ ሆነው መድረኩን ተረክበዋል፡፡

አጀንዳ 4. የማህበሩን ከሐምሌ 1/2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም የ6 ወራት የሽግግር ግዜ ክንውን ሪፖርት መርምሮ መወመሰን

የማህበሩ 16ኛ ዙር ጠቅላላ ጉባኤ የማህበሩን መተዳደሪያ ደንብ በማሻሻል የማህበሩ የበጀት ዓመት እንደ ኤ.አ.አ ከጃንዋሪ 1 እስከ ዲሴምበር 31 እንዲሆን በመወሰኑና ይህም የበጀት ዓመት የሚጀምረው ከጃንዋሪ 1/2023 ጀምሮ በመሆኑ ከኢትዮጵያዊያን አቆጣጠር ወደ አውሮፓውያን አቆጣጠር መሸጋገሪያ ከሀምሌ 1/2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም የ6 ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት አጠር ባለመልኩ በንባብ ቀርቧል፡፡   

በመቀጠል ከጉባኤው አባላት፡- ማህበሩ ብዙ ተግዳሮቶች ያሉበት ቢሆንም አንጋፋ ማህበር ስለሆነ ድክመቶቹን ብቻ ሳይሆን ጥንካሬውንም አንስቶ ማመስገን ይገባል፤ በወላይታ ምርጫ ቅሬታ ላይ የተወሰደው እርምጃ ትክክለኛ ነው፤ ማህበሩ ሴቶችን ለማሳተፍ በሚያደርገው ጥረት ሊመሰገን ይገባል፤ ከምርጫው በፊት ሶስት ቀን ስልጠና አንድ ቀን ምርጫ ተብሎ የተደረገው ግን ምርጫውም ስልጠናውም አንድ ቀን ስለሆነ ይህ መስተካከል አለበት፤ እስከ 4ኛ ክፍል የነበረው የወላይታ ሶዶ አይነስውራን ት/ቤት እስከ 5ኛ ክፍል መሆኑ ጥሩ ስለሆነ ወደፊትም እስከ 6ኛ ሊቀጥል ይገባል፤ በአዲስ አበባ እና በአዳማ ላይ የሚታይ ስራ ሲኖር 250 አባላት ያሉት ሰበታ ላይ ግን ለምን ስራ አይሰራም? ወደፊትስ ለሰበታ ምን ታቅዷል? ከሰበታ ምርጫ ጋር በተያያዘ ወደፊት በኮሚቴ ይታያል የተባለው ግልጽ አይደለም፤ ትግራይ የምንገኝ አባላት ከማህበሩ የምናገኘው ጥቅም የለም፤ እየተዘነጋን ነው፤ እቅድና ሪፖርቱ ስለመጣጣሙ እርግጠኛ መሆን ስለማይቻል ወደፊት ተስተካክሎ መቅረብ አለበት፤ ዲዛይኑ ሳይሰራ ባለ16 ወለል ህንጻ የሚለው እንዴት ሊታወቅ ቻለ? በአባልነት ያልታቀፉ አባላት ሊታቀፉ ይገባል፤ በርካታ ስልጠናዎች ሲሰጡ ግብረመልስ አለን ወይ? አንዲት ሴት ብቻ እየተሳተፈች አካታች ነው ማለት እንዴት ይቻላል? የቅርንጫፎች ሪፖርት ለምን አልቀረበም? ቅርንጫፎቹ ምን ላይ እንዳሉ አይታወቅም፤ ብዙ ችግሮች ለምሳሌ የአደረጃጀት ችግር ስላለ መጪው አመራር እና አባሉ ሊሰሩበት ይገባል፤ የሚሉ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡

በተነሱት ሃሳቦች ላይ ከስራ አመራር ቦርድ በተሰጠው ምላሸ፡- ከስልጠናና ምርጫ ጋር በተያያዘ ግማሽ ቀን ስልጠና ግማሽ ቀን ምርጫ እንጂ ከዚህ የተለየ መልእክት አለመሰራጨቱ፤ ከወላይታ አዳሪ ት/ቤት ጋር በተያያዘ እድገቱ የሚደገፍ መሆኑን፤ በሰበታ ምንም አልተሰራም ለተባለው የተሰራ መሆኑን ለምሳሌም፡- የምርጫ ስልጠና ፣ 2 ጊዜ የኮምፒዩተር ስልጠና  ተሰጥቷል፤ በኮቪድ ወቅትም ድጋፍ የተደረገ ሲሆን አባላት ብዙ ስለሆኑ ላይዳረስ እንደሚችል፤ በአንጻራዊነት ግን ትግራይና ሰሜን ጎንደር ግን ምንም ያልተሰራ መሆኑ፤  በአዳማ በ2 ት/ቤቶች ላይ ስራ የሚሰራ ሲሆን ይህም የለጋሾቹ ፍላጎት መሆኑን፤ ሰበታ ከሌሎች የተሻለ ድጋፍ ያለው ሲሆን ቅርንጫፉ ደግሞ ፕሮጀክቶች እንዲቀረጹ  ሊያደርግ እንደሚችል፤ የሰበታ ምርጫ ብዙ ጊዜ መልስ የተሰጠበትና 6 ተመራጮች ያሉት ሲሆን በአንድ ግለሰብ ላይ ለቀረበው ቅሬታ ምላሽ  መሰጠቱ፤ ከትግራይ ጋር በተያያዘ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ለመቅረጽ ጥረት እየተደረገ ሲሆን ለሰቆጣና ለሁለት የትግራይ ከተሞች ፕሮጀክት ተቀርጾ  መግባቱን፤ ቶፊ ላይ ትግራይ ያልተካተተው በረጂዎች ፍላጎት ምክንያት ሲሆን በጦርነቱ ምክንያትም ትግራይ ላይ ሊሰራ አለመቻሉ፤ ይሁንእንጂ መጠኑ ቢያንስ በኮቪድ ወቅት ለትግራይ መጠነኛ ድጋፍ መደረጉ፤ ሪፖርቱ ተሟልቶ የተዘጋጀ ሲሆን ለማሳጠር ሲባል ከቀረበበት መንገድ የተፈጠረ ችግር መሆኑን፤ የህንጻውን መጠን በተመለከተ ቦታው እራሱ ስለሚወስነውና በእስኬማቲክ ዲዛይኑ ሊታይ የሚችል መሆኑ፤ የቅርንጫፎች ሪፖርትን በተመለከተ በርካታ ቅርንጫፎች ሪፖርት የመላክ ችግር ያለባቸው መሆኑ፤ ማህበራት መቋቋማቸው የማያሰጋ እና ማህራችንም አብሮ መስራት የሚችል ሲሆን ማህበሩ አንጋፋ እና ህጋዊ ማህበር በመሆኑ የራሱን አላማ ለማስፈጸም የሚሰራ መሆኑን ነገር ግን ክፍተቶችን ለመድፈን አደረጃጀትን በተመለከተ መጪው አመራር ጥናት በማድረግ ለቀጣይ ስብሰባ ሊያቀርብ እንደሚገባ በማብራራት ምላሽ ተሰጥቷል፡፡

ከዚህ በኋላ በሪፖርቱ ላይ በተሰጠው ድምጽ በ55 ድምጽ ድጋፍ በ3 ተቃውሞ እና በ2 ድምጸ ተአቅቦ ሪፖርቱ ጸድቋለወ፡፡

አጀንዳ 5. የማህበሩን ከሐምሌ 1/2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም የ6 ወራት የሽግግር ግዜ ሒሳብ መግለጫ እና በውጭ ኦዲተር የተመረመረ የኦዲት ሪፖርት መርምሮ መወሰን

በውጭ ኦዲተር የተመረመረ የማህበሩ የ2014 ዓመታዊ እና የ2015 የመሸጋገሪያ የ6 ወራት የኦዲት ሪፖርቶች በካሳዬ አሰፋ የተመሰከረለት የኦዲት ድርጅት ቀርቧል፡፡ በሪፖርቱ ላይ ከቤቱ የሚከተሉት ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ የአንዳድ ቦታ የሂሳብ ሚዛኑ ትክክል ነው ወይ? የአክስዮን ሼር በትክክል ተመዝግቧል? ለህንጻ ግንባታ 20 ሚሊዮን እንደተሰበሰበ ስለተሰማ ተመዝግቧል ወይ? ማህበሩ በግንባታ ላይ ለምን አልሰራም? 16 ሚሊዮን አልተዋጠልኝምና እንዴት ነው? አቅም ግንባታ የተሰጠው ለማን ነው? ተሰብሳቢ የተባለው ምን አይነት ነው? ስቶክንስ ይጨምራል ወይ? ቶፊ ፕሮጀክት ስለሆነ እንዴት ከማህበረቡ አካውንት ውስጥ ይካተታል? አንዳንድ ወጪዎች ለአካል ጉዳተኛ ሲሆን ፕሮግራም ስለሚሆኑ ታይቷል ወይ? አሻሚ የተባሉት ምንድን ናቸው? ቃለ ጉባኤ ይያዛል ወይ? አንድ ኦዲተር ምን ያህል ጊዜ ኦዲት ያደርጋል የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡

በኦዲተሩና በስራ አመራር ቦርድ በተሰጠው ምላሽ  የሂሳብ ሚዛኑ በአግባቡ መሆኑን እና 20/80 ከወጪው እንጂ ከገቢው አለመሆኑ፤ የአክሲዮን ሼር በትክክል መመዝገቡን ፤ የህንጻ ግንባታ 20 ሚሊዮን የተባለው ኦዲተሩን የማይመለከትና በማህበሩ በኩል ግን ለግንባታው የተሰበሰበ ብር እንዳለ እሱም ለጉባኤው ቀርቦ እንደሚወሰን ፤ የማህበሩ ግንባታን በተመለከተ ለቀረበ ጥያቄ ህንጻ ለመገንባት ጥረት እየተደረገ መሆኑ 16 ሚሊዮን የፕሮግራም ወጪ ከህጉ አኳያ በትክክል ወጪ መደረጉን፤ አቅም ግንባታ በተመለከተ በክንውን ሪፖርት ውስጥ ለማን እንደሆነ የሚገለጽ እንጂ ኦዲተሩ የሚያየው በተገቢው መንገድ ስለመውጣቱ መሆኑን፤ ተሰብሳቢ የሚባለው ከ6 ወር አይብለጥ እንጂ ስራ ስለማይቆም ለስራ የወጡ፤ በሰው እጅ ያሉ ያልተወራረዱ ገንዘቦች መሆናቸውን፤ የኦዲት ሪፖርቱ ስቶክንም እንደሚጨር እና ኢንቨንተሪም የተካሄደ መሆኑን፤ ቶፊ ፕሮጀክት ቢሆንም በአመቱ መጨረሻ ላይ የተወሰነ ገንዘብ ለተከታዩ ዓመት ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ ፕሮጀክቶች እንደአጀማመራቸው አመቱን ሊያሳልፉ እንደሚችሉ ሆኖም የማህበሩ ሒሳብ ሆነው የሚሰሩ መሆናቸውን ፤ የፕሮግራም ወጪን በተመለከተ ህጉ በሚያዘው መሠረት መሠራቱን፤ አሻሚ የተባለው አንዳንድ ስራዎች የፕሮግራምና የአስተዳደራዊ እንጂ በሒሳቡ ላይ አሻሚ ነገር የሌለ መሆኑ ፤ ቃለጉባኤ እየተያዘ መሆኑ፤ አንድ ኦዲተር አሁን ባለው ሁኔታ  ገደብ እንደሌለው ሲገለጽ ከባለስልጣኑ የገተኙት ታዛቢ ይህን በተመለከተ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የተገኙት ታዛቢ አንዳንድ ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን ሰጥተው የማብራሪያ መልስ ከኦዲተሩና ከምክትል ፕሬዘዳንቱ ከተገለጸ በኋላ የኦዲት ሪፖርቱ በ63 ድምጽ ድጋፍ ያለምንም ተቃውሞ በ6 ተአቅቦ ጸድቋል፡፡

አጀንዳ 6. የውስጥ ኦዲተር ስለሚሾምቦት ሁኔታ ተወያይቶ መወሰን

እዚህ አጀንዳ ላይ በተሰጠው ማብራሪያ በማህሩ መተዳደሪያ ደንብ ካሉት የሃላፊነት ቦታዎች አንዱ የውስጥ ኦዲተር ሲሆን የውስጥ ኦዲተርን የሚሾመውና ክፍያውንም የሚወስነው ጠቅላላ ጉባኤው መሆኑን፤ ተጠሪነቱም ለጠቅላላ ጉባኤው መሆኑን፤ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ የማህበሩ ስራ እየሰፋ በመሆኑ የውስጥ ኦዲተር አስፈላጊ መሆኑ፤ ነገር ግን ጠቅላላ ጉባኤው በቀላሉ የውስጥ ኦዲተር መሾም ስለሚቸገር ለስራ አመራር ቦርዱ ውክልና ሰጥቶ የሥራ አመራር ቦርዱ የውስጥ ኦዲተሩን ቀጥሮ ለቀጣዩ የጉባኤ ስብሰባ ሪፖርት እንዲያደርግ መታሰቡ ተብራርቷል፡፡

 በዚህ የውሳኔ ሃሳብ ላይ በተሰጠው ድምጽ በ56 ድጋፍ በ6 ተቃውሞ እና በ2 ድምጸ ተአቅቦ ሃሳቡ ጸድቋል፡፡

አጀንዳ 7. ለህንጻ ግንባታ የሚውል መነሻ ገንዘብ መወሰን

ይህ አጀንዳ የቀረበው ማህበሩን ለግንባታ ያሰባሰበውን ብር በአግባቡ መጠቀም እንዲችልና ለግንባታው ብቻ እንዲውል ለመወሰን በመሆኑ በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ለሚገነባው ህንጻ 20.7 ሚሊዮን ደሴ ለሚገነባው ህንጻ 4 ሚሊዮን እንዲወሰንና ለሌላ ለምንም አላማ ይህ ገንዘብ እንዳይወጣ ጉባኤው እንዲወስን አስቦ መሆኑ ተብራርቷል፡፡

በዚህም መሰረት በተሰጠው ድምጽ በ55 ድጋፍ በ1 ተቃውሞ እና በ4 ድምጸ ተአቅቦ የተጠቀሰው ገንዘብ ለሌላ አላማ እንዳይውልና ለህንጻዎቹ ግንባታ ብቻ እንዲውሉ ተወስኗል፡፡

አጀንዳ 8. የማህበሩን መተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 17 ትርጉም መስጠት

በዚህ አጀንዳ ላይ በተደረገው ውይይት ስብሰባ ለማካሄድ የግድ በአካል የማይሆንበት የቴክኖሎጂ ደረጃ ላይ መደረሱን እና አስቸጋሪ ሁኔታ ሲፈጠርም በቨርቿል ስብሰባ ማካሄድ ስለሚቻል የግድ በአካል ተደርጎ መተርጎም የለበትም የሚል ሀሳብ ሲቀርብ በተቃራኒው ደግሞ ለቴክኖሎጂ ተደራሽ ያልሆኑ ችሎታውም የሌላቸው ብዙ ስለሆኑ በአሁኑ ወቅት ይህን ማድረግ አይቻልም የሚሉ ሀሳቦች ተንሸራሽረው በመጨረሻ በተሰጠው የትርጉም ድምጽ በአካል መገኘት ብቻ ተደርጎ መተርጎም አለበት የሚለው በ49 ድምጽ ድጋፍ ሲያልፍ በቨርቿል መሆን አለበት የሚለው 16 ድምጽ በማግኘት ውድቅ ሆኗል፡፡ 2 ድምጸ ተአቅቦ ተሰጥቷል፡፡

አጀንዳ 9. የማህበሩን መተዳደሪያ ደንብ ስለሚሻሻልበት ሁኔታ ለቦርዱ አቅጣጫ መስጠት

በዚህ አጀንዳ ላይ በተሰጠው ማብራሪያ አንዳንድ ሊወጡ የሚገቡ ህጎች መኖራቸውን፤ ለምሳሌ፡- የጥቅም ግጭት ሊኖራቸው የሚችሉ በሌሎች ድርጅቶች ውስጥ በቦርድ ሰብሳቢነትና አባልነት ወይም ማህበሩ ከሚሸጣቸው ቁሳቁስ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ንግድ የሚነግዱ በማህበሩ ውስጥ አመራር ከሆኑ ሊከተል የሚችለውን የጥቅም ግጭት መገደብ ማስፈለጉን፤ ነገር ግን ያለጥናት ደንብ ማሻሻል የሚያስከትለው ችግር በመኖሩ ደንቡን ለማሻሻል ቀጣዩ ቦርድ ሃላፊነት ወስዶ ጥናት አድርጎ ለቀጣዩ የጉባኤ ስብሰባ እንዲያቀርቡ ታስቦ መሆኑ ተብራርቷል፡፡

በዚህ የውሳኔ ሃሳብ ላይ በተሰጠው ድምጽ በ58 ድጋፍ በ3 ተቃውሞ እና በ1 ድምጸ ተአቅቦ ጸድቋል፡፡

አጀንዳ 10. የማህበሩን የቀጣይ 5 ዓመታት መሪ እቅድ ተወያይቶ መወሰን

የማህበሩ የቀጣይ 5 አመታት መሪ እቅድ በአጭሩ ቀርቦ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡

አጀንዳ 11. የማህበሩን የ2023 ዓመታዊ እቅድ እና በጀት መርምሮ ማጽቅ

የማህበሩ የ2023 እቅድ ከቀረበ በኋላ ከቤቱ በተሰጠው አስተያየት ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል የለም፤ ለምሳሌ ደሴ ግማሽ በጀት ተፈቅዶ በዚህ እቅድ ውስጥ አልተካተተም ባዶ በሆነው የደሴ ቦታ ላይ በውል እንድንሰራበት ይደረግ፤ የደሴ ህንጻ ከ4 ወለል በላይ የሚያሰራ መሆኑ በባለሙያዎች ስለተገለጸ ሊጨመር ይገባል፤ እንደ ነጭ በትር እና ብሬል በዓላት ባሉ ክብረ በዓላት በመጠቀም መንገድ ላይ በመውጣት የግንዛቤ ስራ ይሰራ፤ የዓይነስውራን የዩንቨርሲቲ መግቢያ ጉዳይ ህግ ይውጣለት፤ ማህበሩ ሊያስገነባ ላሰበው ህንጻ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ጭምር መዋጮ ስለሚያደርጉበት ሁኔታ ሊካተት ይገባል፤ በኦሮሚያ ክልል ማህበሩ አደጋ ላይ ስላለ እርምጃ ይወሰድ የሚሉ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡

ከስራ አመራር ቦርድ እና ከጽ/ቤቱ በተሰጠው የማብራሪያ ሃሳብ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ለሁሉም ማዳረስ እንደማይቻልና ደሴ ግን ግማሽ በጀት ብቻ ሳይሆን ከደሴ የሚገኘው ገቢ ሙሉ በሙሉ ለህንጻ ግንባታው እንዲውል መወሰኑ ክፍት በሆነው ቦታ ላይ ስራ መስራትን በተመለከተ የማህበሩ ተቀጣሪ እና የቅርንጫፍ ኮሚቴ አባላት በመኖራቸው ከነሱ ጋር መስማማት እንደሚቻል የህንጻውን ርዝመት በተመለከተ ዲዛይን ሲሰራ ሊረጋገጥ እንደሚችል፤ የነጭ በትር እና የብሬል ቀንን በተመለከተ ሃሳቡ ጥሩ ሆኖ የለጋሾችም ሃሳብ ግምት ውስጥ ሊገባ እንደሚገባ፤ የዩንቨርሲቲ መግቢያ በተመለከተ ለአባላት ከሚሰጠው አወንታዊ ድጋፍ ጋር የሚያያዝ መሆኑን፤ ሊገነባ ለታሰበው ህንጻ የሚደረገውን መዋጮ በተመለከተ የሃብት አሰባሳቢ ኮሚቴ እንደሚሰራው፤ በኦሮሚያው ያሉ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት የሚፈጥሩት ችግር በሌሎችም ክልሎች ጭምር እየታየ ስለሆነ ህጋዊ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ተብረርቷል፡፡ በመጨረሻም በእቅዱ ላይ በተሰጠው ድምጽ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡

አጀንዳ 12. የአማካሪ ቦርድ መመሪያ መርምሮ መወሰን

የአማካሪ ቦርድ መመሪያን በተመለከተ ጉባኤው በስፋት ለመመልከት ስለማይችል የስራ አመራር ቦርዱ እንዲወስን በሙሉ ድምጽ ለስራ አመራር ቦርዱ ውክልና ተሰጥቷል፡፡

አጀንዳ 13. የ17ኛ ዙር ስራ አመራር ቦርድ ምርጫ ማከናወን

ለዚህ አጀንዳ በቅድሚያ የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 19፣ አንቀጽ 33 እና አንቀጽ 34 በንባብ ተሰምቷል፡፡ በቅድሚያ ተባባሪ አባል መመረጥ ስላለበት የማህበሩ ጽ/ቤት ያሉትን ተባባሪ አባላት ማንነት ጭምር በመዘርዘር አቅርቧል፡፡

ሆኖም በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 11 መሰረት ተባባበሪ አባላት የጉባኤ አባል ስለሚሆኑበት መንገድ ጉባኤው ዝርዝር መመረያ እንደሚያወጣ ስለተገለጸ እና ጉባኤው ደግሞ ዝርዝር መመሪያ ስላላወጣ ከዚህ የተነሳ የጉባኤ አባል የሆኑ ተባባሪ አባላት በሌሉበት ሁኔታ መምረጥ እንደማይቻል ሃሳብ ቀርቦ ከሰፊ ክርክር በኋላ በማህሩ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 9 መሠረት ከውጪ መሳብ ስለመቻል አለመቻሉ እንዲወሰን ሀሳብ ቀርቦ ከውጪ አሁን መሳብ የለብንም ቦታው ክፍት ሆኖ ለተከታዩ የጉባኤ ስብሰባ ሊቀርብ ይገባል የሚለው 32 ድምጽ አግኝቶ ሲያልፍ አሁኑኑ ሊመረጥ ይገባል የሚለው 28 ድምጽ በማግኘት ውድቅ ሆኗል፤ 6 ድምጸ ተአቅቦ ተደርጓል፡፡ በመቀጠል በዚሁ በአንቀጽ 34 ንኡስ አንቀጽ 9 መሠረት የጉባኤ አባላት ካልሆኑት መካከል ስለመሳብ እና አለመሳብ በተሰጠው ድምጽ በአሁኑ ጊዜ ከውጪ መሳብ የለብም የሚለው 33 ድምጽ አግኝቶ ሲያልፍ ከውጪ እንሳብ የሚለው 30 ድምጽ አግንቶ ውድቅ ሆኗል፤ 4 ድምጸ ተአቅቦ ተደርጓል፡፡

በመቀጠል የአስመራጭ ኮሚቴ ለመምረጥ በተካሄደው የእጩዎች ጥቆማ 3 እጩዎች ቀርበዋል፡፡ እነርሱም አቶ አማረ ብዙነህ፣ አቶ አበረ ሃብተወልድ እና ወ/ሮ እመቤት ጌትነት ሲሆኑ አቶ አማረ ብዙነህ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ጌትነት ጸሐፊ አቶ አበረ ሃብተወልድ አባል ሆነዋል፡፡

የአስራጭ ኮሚቴው ሃላፊነቱን ተረክቦ ስለምርጫው ሂደት በተደረገው ውይይት የአዲስ አበባ ተወካዮች 4 በመሆናቸው 8 እጩዎችን እንዲያቀርቡ ክልሎች ደግሞ ለ4 ተመራጮች 16 እጩዎችን እንዲያቀርቡ ስምምነት ላይ ተደርሶ ጥቆማው የሚካሄደው ግን በጋራ ይሁን ወይስ በተናጥል ይሁን በሚለው ላይ ድምጽ ተሰጥቶ በጋራ ይሁን የሚለው በ38 ድምጽ ድጋፍ ሲያልፍ በተናጥል ይሁን የሚለው 22 ሆኖ በ2 ድምጸ ተአቅቦ ወድቋል፡፡ ከዚህ በኋላ ከክልሎች የሚከተሉት እጩዎች ተጠቁመዋል

1ኛ አቶ ሀፍቱ ካህሳይ 2ኛ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ 3ኛአቶ የማነ ዮሐንስ 4ኛ አቶ በለጠ ሺበሺ 5ኛ አቶ ካሳሁን አሰፋ 6ኛ አቶ ጫላ ጉደታ 7ኛ ወ/ሪት ፍሬህይወት መዝገበ 8ኛ ወ/ሮ ስመኝ ሲዳ 9ኛ አቶ ኩማ አሊ 10ኛ አቶ ዮሐንስ ካህሳይ 11ኛ ወ/ሮ አማረች ወዳሎ 12ኛ አቶ ቢላል ከቢርሁሴን 13ኛ ወ/ሮ ለምለም አሰፋ 14ኛ አቶ አንድነት ዘነበ 15ኛ አቶ ዘሪሁን አማረ 16ኛ ወ/ሮ ነፍሴ ናኒሳ ሆነዋል፡፡ ከክልል ከተጠቆሙት መካከል ወ/ሪት አበባ ጽጌ የ11ኛ ክፍል ተመሪ መበሆናቸውና በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ በአንቀጽ 33 ንዑስ አንቀጽ 12 መሠረት በአካባቢያቸው ቢያንስ ለ3 ዓመት ሊቆዩ ስለመቻላቸው ማስረጃ ስለሌለ ከእጩነት ተሰርዘዋል፡፡ አቶ ሮምሃ ወልዱ በእጩነት ተጠቁመው የነበረና ከ10 በመቶ በላይ ድጋፍም አግኝተው የነበረ ቢሆንም በአንቀጽ 33 ንዑስ አንቀጽ 5 መሠረት ተወክለው ከመጡበት አካባቢ በአባላቱ ተደማጭነት ስለሌላቸው ለእጩነት መቅረብ እንደሌለባቸው ተቃውሞ ቀርቦ ተጠቋሚው ምላሽ እንዲሰጡ እድል ተሰጥቷቸዋል፡፡ እርሳቸውም ተቃውሞ አቅራቢው ስብሰባ ባለመጥራታቸው ሊሰሩ እንዳልቻሉና እንዳይሰረ ግፊት እንደሚያደርጉባቸው በማስገንዘብ የመከላከያ ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡

በማኅበሩ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 5 መሠረት ተቃውሞ የቀረበባቸው አባል ለዕጩነት ለማለፍ ከተሰብሳቢው ቢያንስ በ1/3 መደገፍ ስላለባቸውና የድምጽ ሰጪዎቹ ቁጥር 70 በመሆኑ 24 እንዲያመጡ ስለሚጠበቅባቸው በተሰጠው የድጋፍ ድምጽ 22 በማምጣታቸው ለእጩነት ሳይልፉ ቀርተዋል፡፡ ሌላው ተጠቋሚ አቶ መሐመድ ከድር ለጥቆማ ቢቀርቡም በእጩነት ለማለፍ 10% ማለትም 7 ድምጽ ባለማግኘታቸው ወድቀዋል፡፡

ከአዲስ አበባ የተጠቆሙት እጩዎች ደግሞ

1ኛ አቶ ተስፋው አወቀ 2ኛ ወ/ሪት ቃልኪዳን ሽመልስ 3ኛ ወ/ሮ ማሜ ግርማ 4ኛ አቶ ፋንታሁን መንግስቴ 5ኛ ወ/ሮ ሃረገወይን አለነ 6ኛ አቶ ለገሠ ሃ/ማርያም 7ኛ አቶ አበራ ረታ 8ኛ አቶ አያኖ ደቻሳ እጩ ሆነው ቀርበዋል፡፡

ከአዲስ አበባ ተወካዮች መካከል አቶ ዮሐንስ ኪዳኔ ተጠቁመው ለእጩነት ለማለፍ በ10% ተደግፈው የነበረ ቢሆንም ተቃውሞ ቀርቦባቸዋል፡፡ የቀረበባቸውም ተቃውሞ በ2007 ዓ.ም ከአንድ ግለሰብ ጋር በመመሳጠር ከማኅበሩ ሰነድ አስወጥተው ውጪ እያነበቡ ለሀገር ውስጥ ገቢ ጥቆማ ሰጥተው ማህበሩን አስቀጥተው ለራሳቸው ኮሚሽን የበሉ በመሆናቸው በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 33 ንዑስ አንቀጽ 2 መሰረት በመልካም ስነምግባር እንዲታወቁ ስለማያደርጋቸው በእጩነት መቅረብ የለባቸውም የሚል ነው፡፡ እሳቸውም ለቀረበባቸው ተቃውሞ ምላሽ እንዲሰጡ እድል ተሰጥቷቸው፡- በህግ የማይደራደሩ በመሆናቸው ህግን ለማስከበር ሲሉ እርምጃውን መውሰዳቸውን፣ ተቃውሞ አቅራቢው እራሳቸው ፈርመው እንደነበረ ገልጸው ራሳቸውን ተከላክለዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ተቃውሞ የቀረበባቸው ተጠቋሚ በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 5 መሠረት በእጩነት ለማለፍ ከተሰብሳቢው  የ1/3 ድምጽ ማግኘት ስሊገባቸው፣ የተሰብሳቢዎቹ ድምጽ ደግሞ 70 በመሆኑና ከላይ በተጠቀሰው መሰረት ቢያንስ በ24 ድምጽ ሊደገፉ ስለሚገባ ለተሰብሳቢው የድጋፍ ድምጽ ተጠይቆ 22 በማግኘታቸውና ተፈላጊው ዝቅተኛ ቁጥር 24 ባለማግኘታቸው በእጩነት ሳያልፉ ቀርተዋል፡፡

ከዘህ በኋላ ከእጩነት ያለፉት 24ቱም እጩዎች ስለራሳቸው ለተሰብሰቢው ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በየአንዳንዱ እጩ ስም ፖስታ ተዘጋጅቶ ለእያንዳዱ መራጭ 8 ካርድ ከታደለ በኋላ ከመራጮች እጅ ተሰብስቦ በእጩዎቹ ፖስታ የገባው ካርድ በእጩዎቹና በታዛቢዎች ፊት ተከፍቶ ተቆጥሯል፡፡ በውጤቱም፡-

1ኛ አቶ አበራ ረታ ከአዲስ አበባ 43 ድምጽ 2ኛ አቶ ፋንታሁን መንግስቴ ከአዲስ አበባ 40 ድምጽ 3ኛ አቶ ሀፍቱ ካህሳይ ከአማራ 34 ድምጽ 4ኛ አቶ ተስፋው አወቀ ከአዲስ አበባ 28 ድምጽ 5ኛ አቶ በለጠ ሺበሺ ከአማራ 27 ድምጽ በድጋሚ 5ኛ ወ/ሪት ቃልኪዳን ሽመልስ ከአዲስ አበባ 27 ድምጽ 6ኛ ወ/ሪት ፍሬህይወት መዝገበ ከአማራ 26 ድምጽ 7ኛ ወ/ሮ ሀረገወይን አለነ ከአዲስ አበባ 25 ድምጽ 8ኛ አቶ አያኖ ደቻሳ ከአዲስ አበባ 23 ድምጽ 9ኛ አቶ ካሳሁን አሰፋ ከወላይታ 20 ድምጽ 10ኛ አቶ አንድነት ዘነበ ከድሬደዋ 18 ድምጽ በድጋሜ 10ኛ  አቶ ጫላ ጉደታ  ከኦሮሚያ 18 ድምጽ እንደገና 10ኛ አቶ የማነ ዮሐንስ ከትግራይ 18 ድምጽ 11ኛ አቶ ለገሰ ሃ/ማርያም ከአዲስ አበባ 17 ድምጽ 12ኛ ወ/ሮ ነፍሴ ናኒሳ ከሀዋሳ 16 ድምጽ 13ኛ ወ/ሮ አማረች ወዳሎ 14 ድምጽ በድጋሚ 13ኛ አቶ ዘሪሁን አማረ ከአሰላ 14 ድምጽ 14ኛ. አቶ ዮሐንስ ካህሳይ ከትግራይ 13 ድምጽ 15ኛ ወ/ሮ ለምለም አሰፋ ከትግራይ 12 ድምጽ በድጋሚ 15ኛ ኩማ አሊ ከሀረር 12 ድምጽ 16ኛ. ማሜ ግርማ ከአዲስ አበባ 11 ድምጽ በድጋሜ 16ኛ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ከደብረብርሃን 11 ድምጽ 17ኛ አቶ ቢላል ሁሴን ከኦሮሚያ 10 ድምጽ 18ኛ ወ/ሮ ስመኝ ሲዳ ከድሬደዋ 6 ድምጽ አግኝተው 76 ካርድ በድምጸ ተአቅቦ ተመላሽ ተደርጓል፡፡

ከአዲስ አበባ 4 ከክልል ደግሞ 4 እንዲሁም ቢያንስ 3 የሴቶች ተሳትፎ በማቻቻል 1ኛ አቶ አበራ ረታ ከአዲስ አበባ በቀጥታ አባል 2ኛ አቶ ፋንታሁን መንግስቴ ከአዲስ አበባ በቀጥታ አባል 3ኛ አቶ ሀፍቱ ካህሳይ ከአማራ በቀጥታ አባል ሲሆኑ የ3 ሴቶችን ቦታ ለመያዝ 27 በማምጣት 5ኛ የሆኑት ወ/ሪት ቃልኪዳ ሽመልስ ከአዲስ አበባ 26 ድምጽ በማምጣት 6ኛ የሆኑት ወ/ሪት ፍሬህይወት መዝገበ እና 25 ድምጽ ያመጡት ወ/ሮ ሀረገወይን አለነ የሴቶችን ቦታ በመሙላት የስራ አመራር ቦርዱ አባል ሆነው ሲልፉ በሴቶቹ ምክንያት ከአዲስ አበባ 4ኛ የሆኑት አቶ ተስፋው አወቀ የቦርዱ አባል መሆን ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ በተጨማሪም ከአንድ ክልል ከ2 በላይ የቦርድ አባላት ሊመረጡ እንደማይችሉ በሚደነግገው የማህበሩ ደንብ መሰረት ከአማራ ክልል 34 ድምጽ ያገኙት አቶ ሀፍቱ ካህሳይ በማለፋቸው እና በሴትነታቸው ምክንያት 26 ድምጽ ያገኙት ወ/ሪት ፍሬህይወት መዝገበ ከአማራ ክልል በማለፋቸው ከአማራ ክልል 27 ድምጽ አግኝተው የነበሩት አቶ በለጠ ሺበሺ የስራ አመራር ቦርድ አባል ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ ከክልሎች 20 ድምጽ በማምጣት ቀጣይ የሆኑት አቶ ካሳሁን አሰፋ ከወላይታ በቀጥታ የስራ አመራር ቦርድ አባል ሲሆኑ ከክልል 4ኛውን አባል ለመወሰን ግን 3 እጩዎች እያንዳንዳቸው 18 ድምጽ በማምጣታቸው በ3ቱ ላይ ድጋሜ ድምጽ ተሰጥቶ አቶ አንድነት ዘነበ ከድሬደዋ በ27 ድምጽ የስራ አመራር ቦርድ አባል ሆነው ሲያልፉ አቶ የማነ ዮሐንስ በ21 ድምጽ እና አቶ ጫላ ጉደታ በ17 ድምጽ ተጠባባቂዎች ሆነዋል፡፡

በዚህም መሰረት የ17ኛ ዙር ስራ አመራር ቦርድ 8ቱ አባላት 1ኛ አቶ አበራ ረታ 2ኛ አቶ ፋንታሁን መንስቴ 3ኛ አቶ ሀፍቱ ካህሳይ 4ኛ ወ/ሪት ቃልኪዳን ሽመልስ 5ኛ. ወ/ሪት ፍሬህወት መዝገበ 6ኛ ወ/ሮ ሀረገወይን አለነ 7ኛ አቶ ካሳሁን አሰፋ እና 8ኛ አቶ አንድነት ዘነበ ሆነው ቀደም ሲል በተወሰነው ውሳኔ መሰረት 9ኛው የተባባሪ አባል ቦታ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡

የስራ አመራ ቦርዱ አባላት በመካከላቸው ባደረጉት የሃላፊነት ድልድል አቶ አበራ ረታ የቦርዱ ሰብሳቢ እና የማህበሩ ፕሬዘዳንት፣ አቶ ፋንታሁን መንግስቴ የቦርዱ ም/ሰብሳቢ እና የማህበሩ ም/ፕሬዘዳንት ሆነው ለጉባኤው ቀርቦ ጸድቋል፡፡

በመጨረሻም ስለሁለቱ ቀናት የጉባኤው ስብሰባ የተወሰኑ አባላት አስተያት ከሰጡ እና የቀድሞ የማህበሩ ፕሬዘዳንት ስብሰባው እንዲሳካ ጥረት ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋና ካቀረቡ በኋላ የሁለቱ ቀን ስብሰባ ተጠናቋል፡፡

Saturday May 27th, 2023 News

ኢናብ ቴክ ክፍል 41 – በአውዳሲቲ ድምጽ ማስገባት፣ ማርተእ እና ማስቀመጥ

Play

download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ዊንዶውስ በሚያዚያ ወር የለቀቀው አፕዴት የጉግል ክሮም አንድ አገልግሎት እንዳይሰራ ያደረገው ስለመሆኑ እና ሞንታና የተባለችው የአሜሪካ ግዛት ቲክቶክን ለብቻዋ ብሎክ እንዲደረግ ስለማገዷ የሚሉትን እንመለከታለን።
በኮምፒውተር ቲፕስ ኤንድ ትሪክስ፣ በአውዳሲቲ አጠቃቀም ድምጽን እንዴት እንደምናስገባ፣ ኤዲት እንደምናደርግ እና ሴቭ አደራረግ በሚሉት ላይ በዛሬው ክፍል እናተኩራለን።
በመሰረታዊ ክፍል፣ ስለስክሪን ሪደርስ የጃውስን አጠቃቀም በሚያብራራው ዝግጅቴ ጽሁፍን እንዴት እንደምናነብ የምንመለከት ይሆናል።
በአድማጮች አስተያየትም ስለቲክቶክ፣ ስለቪዲዮ ኤዲተር፣ ስለጂሺዎ፣ ስለጉግል ክሮም፣ ስለዩኒግራም እና ስለዶትወከር ከአድማጮች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቻለሁ።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሱትን አውዳሲቲን ከዚህአውዳሲቲ ኤንቪዲኤ አድኦንን ከዚህ ጂሺዎ ትንሹን ከዚህ ያውርዱ።

This podcast is powered by Pinecast.

Monday May 22nd, 2023 Podcasts

ኢናብ ቴክ ክፍል 40 – አውዳሲቲ የድምጽ መቅረጫ እና ማርተኢያውን መተዋወቅ

Play

download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ጂሺዎ በቨርዥን 2023-05-06 ስላሻሻላቸው ነገሮች፣ ፋየርፎክስ ዊንዶውስ ሰባትን አልተውም ስለማለቱ፣ በተጠቃሚዎች ብዛት ደረጃዎችን ስለያዙት የዊንዶውስ ቨርዥን እና ብራውዘሮች እንዲሁም ዊንዶውስ 10 ያበቃለት መሆኑን ማይክሮሶፍት አስታወቀ የሚሉትን መረጃዎች እንመለከታለን።
በኮምፒውተር ቲፕስ ኤንድ ትሪክስ፣ አውዳሲቲ የሚባለውን አፕ ማስተዋወቅ ጀምሬ ስለምንነቱ እና ስለአጫጫኑ በዛሬው ክፍል እነግራችኋለሁ።
በመሰረታዊ ክፍል፣ ስለስክሪን ሪደርስ የጃውስን አጠቃቀም ቀጣይ ክፍል ይዤ ቀርቤ ስለአከፋፈቱ እና ስለአዘጋጉ እንመለከታለን።
በአድማጮች አስተያየትም ጂሺዎ በስልካችሁ በድንገት ጸጥ እያለ ለሚያስቸግራችሁ የተወሰነ ምላሽ ተካቷል።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሱትን አውዳሲቲን ከዚህአውዳሲቲ ኤንቪዲኤ አድኦንን ከዚህ ጂሺዎ ትልቁን ከዚህ ያውርዱ።

This podcast is powered by Pinecast.

Thursday May 18th, 2023 Podcasts

ኢናብ ቴክ ክፍል 39 – በዶትወከር ወደምንፈልገው ቦታ በተግባር መድረስ

Play

download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ጃውስ በቨርዥን 2023 ኤፕሪል አፕዴት ስላሻሻላቸው ነገሮች፣ የማይክሮሶፍት ቴክኒሻን ለማይክሮሶፍት ደንበኛ ዊንዶውስን ክራክ ሲያደርግ ስለመገኘቱ እና ቲክቶክ በተጨማሪ ሀገሮች ብሎክ እየተደረገ ስለመሆኑ የሚሉ መረጃዎችን አጋራችኋለሁ።
በሞባይል ወርልድ፣ በዶት ወከር እስካሁን ስንሰበስባቸው የነበሩ የቦታ መረጃዎችን በእንቅስቃሴ ላይ እንዴት እንደምንጠቀምባቸው እንመለከታለን።
በመሰረታዊ ክፍል፣ ስለስክሪን ሪደርስ የጃውስን አጠቃቀም የመጀመሪያ ክፍል ይዤ ቀርቤያለሁ።
በአድማጮች አስተያየትም ስለኮምፒውተር ቫይረሶች ጥንቃቄ የተወሰነ ምላሽ ተካቷል።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሰውን ዶት ዎከር አፕሊኬሽንን ከዚህ ያውርዱ።

This podcast is powered by Pinecast.

Tuesday May 9th, 2023 Podcasts

ኢናብ ቴክ ክፍል 38 – ከኦፕን ስትሪት ማፕ ቦታዎችን ወደ ዶት ወከር ማስገባት እና ራሳችን ቦታዎችን ስለመመዝገብ

Play

download the episode

በዚህ ክፍል፣

በቴክኖሎጂ ነክ መረጃዎች፣ ጂሺዎ በቨርዥን 2023-04-04 ይዟቸው ስለመጣቸው ነገሮች፣ ሜታ የተባለው የፌስቡክ ባለቤት ኩባንያ ትዊተርን የሚፎካከር አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን ስለማስታወቁ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም የምናውቃቸውን ሰዎች ድምጽ በማስመሰል የሚፈጸሙ የማታለል ወንጀሎች እየጨመሩ ስለመሆኑ የሚሉትን መረጃዎች እንመለከታለን።
በሞባይል ወርልድ፣ ዶት ወከር በመጀመሪያ ይዞት ስለመጣው በበጎ ፈቃደኞች ስለሚመዘገበው ኦፕን ስትሪት ማፕ ከሚባለው አገልግሎት የቦታ መረጃ እንዴት እንደምናወርድ እንዲሁም በራሳችን ቦታዎችን እንዴት እንደምንመዘግብ አብራራለሁ።
በመሰረታዊ ክፍል፣ ስለዊንዶውስ ኤክስፕሎረር በሚያብራራው ዝግጅቴ ክፍል ፋይሎችን ከቦታ ቦታ ስለማንቀሳቀስ፣ አዳዲስ ፎልደሮችን ስለመፍጠር እና በሴንድ ቱ ሰብ መኒው ፋይሎችን እንዴት እንደምንልክ እገልጻለሁ።
የአድማጮች አስተያየትም ተካቷል።
ፖድካስቱን ለመከታተል፣ በቴሌግራም https://t.me/enabtechpod ሰብስክራይብ አድርጉ።
ጥያቄ፣ አስተያየታችሁን 0973034577 ላይ የጽሁ፣ የድምጽ ወይም የቴሌግራም መልእክት በማድረግ ልትልኩልኝ ትችላላችሁ።
ቴሌግራም ላይ @enabtechpod እና @enabtechbot በመግባት ትችታችሁን ለመላክ እና አድማጮቼን እንዳውቅ ሰርቬይ ልትሞሉልኝ ትችላላችሁ።
በዝግጅቱ የተጠቀሱትን ጂሺዎ ትልቁን ከዚህጂሺዎ ትንሹን ከዚህ እና ዶት ዎከር አፕሊኬሽኑን ከዚህ ያውርዱ።

This podcast is powered by Pinecast.

Saturday April 22nd, 2023 Podcasts
Skip to content
https://ethionab.org/